Obtenez 3 mois à 0,99 $/mois + 20 $ de crédit Audible

OFFRE D'UNE DURÉE LIMITÉE
Page de couverture de የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

Auteur(s): DW
Écouter gratuitement

À propos de cet audio

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።2025 DW Politique
Épisodes
  • የሕዳር 11 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    Nov 20 2025
    -የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)ና የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረሰ (ኦፌኮ) በኦሮሚያ ክልል ያለዉን የፀጥታ፣ የሕግና ሥርዓት መደፍረስና መፋለሥ ለማቃለል ከክልሉ መሪዎች ጋር መነጋገር እንደሚሹ አስታወቁ።---የጀርመን መንግሥት ለአፍሪቃ ሕብረት አጀንዳ 2063 መርሐ-ግብር ማስፈፀሚያ ተጨማሪ 88 ሚሊዮን ዩሮ ለመርዳት ቃል ገባ።ተጨማሪዉ ገንዘብ አፍሪቃ ዉስጥ ዘላቂ ልማትን፣የአ,ረንጓዴ ኃይልን፣ሠላምና ፀጥታ ለማጠናከርና ለ,ጤና አገልግሎት እንደሚዉል በአዲስ አበባ የጀርመን ኤምባሲ አስታዉቋል።---ሕንድና ፓኪስታን ባለፈዉ ግንቦት የገጠሙት ዉጊያ የፈረንሳይና የቻይናን የጦር መሳሪያ ጥራትና አቅም ለመፈተሽ የዋለ እንደነበር ተነገረ
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • የህዳር10 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    Nov 19 2025
    የህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና «ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» በሚል መጠሪያ የተቀናጁት 5 ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ መንግስት ከምርጫው በፊት በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዲያሰፍን ጠየቁ። ከኤርትራ መሆንዋ ተነገረ የአንዲት እናት የተቆረጡ እጆችን አውራ ጎዳና ላይ ማግኘቱን የጀርመን ፖሊስ ዐሳወቀ። በቦንየተገን ጠያቂዎች ማቆያ የትኖር የነበረው ይህች እናት፣ የት እንዳለች እስከ ትናንት ድረስ እንደማያውቅ ፖሊስ ገልጿል። በሱዳን ጦርነት ጣልቃ በመግባት የምትጠረጠረው የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚደርስባት ወርጂብኝ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ሰ
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • የዓለም ዜና፤ ኅዳር 9 ቀን 2018 ማክሰኞ
    Nov 18 2025
    አርስተ ዜናዎች፤ -ኢሕአፓ ባለፉት 7 ዓመታት በትግራይ ክልል ፣ በአፋር ክልልና በአማራ ክልል፣ አሁን ደግሞ በመላው የአማራ ክልልና በበርካታ የኦሮሚያ ክልል ቀጠናዎች ውስጥ፣ እየደረሱ ያሉ ያላቸውን የወገን ዕልቂትና የመሠረተ ልማት አውታሮች ብሎም የሌሎች ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት ውድመት እንዲቆም ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ጠየቀ።-የሩሲያ ጦር በስድስት የአፍሪቃ ሀገራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የሩሲያ ቴሌቪዥን ዘገበ።-የጀርመን መንግስት የእስራኤል በከፊል አቋርጦት የነበረዉን የጦር መሳርያ አቅርቦት ዉሳኔ እንደሚያነሳ አሳወቀ። በሌላ በኩል የጀርመን ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጥበቃ ተጨማሪ 60 ሚሊዮን ዩሮ ሰጠች።
    Voir plus Voir moins
    11 min
Pas encore de commentaire