Page de couverture de የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

Auteur(s): DW
Écouter gratuitement

À propos de cet audio

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።2025 DW Politique
Épisodes
  • የዓለም ዜና ፤ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ማክሰኞ
    Jul 15 2025
    አርስተ ዜና፤ -የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደ ቻይና እና ህንድ ባሉት የሩሲያ የንግድ አጋሮች ሸቀጥ ላይ እስከ 100 በመቶ የሚደርስ የትራፊ ጭማሪ እጥላለሁ አሉ። የሩሲያ ባለሥልጣናት ግን ይህ እርምጃ ጦርነቱን ከማስቀጠል በቀር ምንም የሚፈይደዉ ነገር የለም ሲሉ አጣጣሉት አጣጥላዋለች።-ድንበር የለሽ ሐኪሞች ድርጅት የተባለዉ ግብረ ሠናይ ድርጅት የዛሬ አራት ዓመት ትግራይ ክልል ዉስጥ ሆነ ተብሎ ስለተገደሉ ሦስት ባልደረቦቹ አሟሟት ያደረገዉን የዉስጥ ምርመራ ዉጤት ዛሬ በይፋ አሰራጨ።-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ከ80 ሺህ በላይ ነዋሪዎች በኦሞ ወንዝ ሙላት መከባባቸውን ነዋሪዎች ገለፁ፡፡
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • የሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    Jul 14 2025
    የሐምሌ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና ሊቢያ ውስጥ በወሮበሎች ተይዘው ሲሰቃዩ የነበሩ ከ100 በላይ ስደተኞች ነጻ መውጣታቸውን ሊቢያ አስታወቀች።ከመካከላቸው 5 ሴቶች ይገኙባቸዋል። የአውሮጳ ኅብረት ከዋሽንግተን ጋር የሚያካሂደው የታሪፍ ንግግር ክልተሳካ 72 ቢሊዮን ዩሮ የሚያወጡ የአሜሪካን ምርቶች የታሪፍ ጭማሪ ዒላማ ሊሆኑ እንደሚችሉ አስጠነቀቀ። ባለፉት ሁለት ወራት ስፔን ውስጥ ከፍተኛ ሙቀት 1,180 ሰዎችን መግደሉን የሀገሪቱ የአካባቢ ሚኒስቴር አስታወቀ። እንደ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዳለው ከሟቾቹ አብዛኛዎቹ እድሜያቸው ከ65 ዓመት በላይ ነው። ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች ናቸው።
    Voir plus Voir moins
    10 min
  • የሐምሌ 06 ቀን 2017 የዓለም ዜና
    Jul 13 2025
    ናይጄሪያ የሽብር እንቅስቃሴ በገንዘብ ይደግፋሉ ያለቻቸውን 44 የቦኮ ሐራም አባላት እስከ 30 ዓመታት በሚደርስ እስራት ቀጣች። በጋዛ ሕጻናትን ጨምሮ ውኃ ለመቅዳት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ 10 ፍልስጤማያውን በተፈናቃዮች መጠለያ ውስጥ በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን የግዛቲቱ የሲቪል ሰዎች ደህንነት ጥበቃ ኤጀንሲ አስታወቀ። የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ ዑን ሩሲያ በዩክሬን ያለውን ግጭት ለመፍታት የምታደርገውን ጥረት ሀገራቸው “ያለ ምንም ቅድመ-ሁኔታ ለመደገፍ” ዝግጁ እንደሆነች ማረጋገጫ ሰጡ። ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ባለፈው አንድ ሣምንት ብቻ ሩሲያ በ1,800 ድሮኖች በዩክሬን ላይ ጥቃት እንደሰነዘረች ተናገሩ።
    Voir plus Voir moins
    9 min

Ce que les auditeurs disent de የዓለም ዜና

Moyenne des évaluations de clients

Évaluations – Cliquez sur les onglets pour changer la source des évaluations.