Épisodes

  • የህዳር10 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    Nov 19 2025
    የህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና «ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» በሚል መጠሪያ የተቀናጁት 5 ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ መንግስት ከምርጫው በፊት በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዲያሰፍን ጠየቁ። ከኤርትራ መሆንዋ ተነገረ የአንዲት እናት የተቆረጡ እጆችን አውራ ጎዳና ላይ ማግኘቱን የጀርመን ፖሊስ ዐሳወቀ። በቦንየተገን ጠያቂዎች ማቆያ የትኖር የነበረው ይህች እናት፣ የት እንዳለች እስከ ትናንት ድረስ እንደማያውቅ ፖሊስ ገልጿል። በሱዳን ጦርነት ጣልቃ በመግባት የምትጠረጠረው የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚደርስባት ወርጂብኝ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ሰ
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • የዓለም ዜና፤ ኅዳር 9 ቀን 2018 ማክሰኞ
    Nov 18 2025
    አርስተ ዜናዎች፤ -ኢሕአፓ ባለፉት 7 ዓመታት በትግራይ ክልል ፣ በአፋር ክልልና በአማራ ክልል፣ አሁን ደግሞ በመላው የአማራ ክልልና በበርካታ የኦሮሚያ ክልል ቀጠናዎች ውስጥ፣ እየደረሱ ያሉ ያላቸውን የወገን ዕልቂትና የመሠረተ ልማት አውታሮች ብሎም የሌሎች ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት ውድመት እንዲቆም ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ጠየቀ።-የሩሲያ ጦር በስድስት የአፍሪቃ ሀገራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የሩሲያ ቴሌቪዥን ዘገበ።-የጀርመን መንግስት የእስራኤል በከፊል አቋርጦት የነበረዉን የጦር መሳርያ አቅርቦት ዉሳኔ እንደሚያነሳ አሳወቀ። በሌላ በኩል የጀርመን ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጥበቃ ተጨማሪ 60 ሚሊዮን ዩሮ ሰጠች።
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • የኅዳር 8 ቀን 2018 ዓም የዓለም ዜና
    Nov 17 2025
    ደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ሰዎች በማርበርግ ተሐዋሲ መሞታቸውን የጤና ሚኒስቴር አረጋገጠ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በያዝነው ዓመት ለሚካሄደው 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቀረበ። የባንግላዴሽ ልዩ ችሎት በቀድሞዋ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ ላይ የሞት ፍድር በየነ። የፖሊስ አዛዡ ደግሞ አምስት ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል። የሱዳን መንግሥት የተመ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ዳርፉር አልፋሸር ውስጥ የተፈጸመውን ጥሰት የሚያጣራ ቡድን ለመላክ መወሰኑን ተቃወመ። በአንጻሩ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል እውነቱን የሚያጣራው የልዑካን ቡድን እንዲላክ ጠይቋል።
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • የህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    Nov 16 2025
    የዛሬው የዓለም ዜና -ሊባኖስ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስራኤል ጦር በሰላም አስከባሪዎች ላይ ተኩስ ከፈተ ማለቱን፤ ብሪታኒያ የስደተኞች ቁጥርን ለመቀነስ የጥገኝነት ፖሊሲ ማሻሻያ ማድረጓን፣ ምዕራብ ጀርመን ውስጥ የሚገኝ አንድ የጨረታ ቤት የሆሎኮስት ዕቃዎችን በሐራጅ ለመሸጥ ማቀዱ በጀርመን ቁጣ ማስነሳቱን፣ግሪክ እና ዩክሬን እስከ መጋቢት 2026 የሚዘልቅ የጋዝ ውል መፈራረማቸውን እንዲሁም በፊሊፒንስ በሙስና ምክንያት ታላቅ ተቃውሞ መቀስቀሱን ያስቃኛል።
    Voir plus Voir moins
    9 min
  • DW Amharic የሕዳር 6 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    Nov 15 2025
    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተው የሔሞራጅ ትኩሳት በሽታ መንስዔ የማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አረጋገጠ። በኢትዮጵያ የሚካሔደው ሀገራዊ ምክክር ያጋጠሙት “አብዛኞቹ ተግዳሮቶች ፖለቲካዊ በመሆናቸው ፖለቲካዊ መፍትሔ” እንደሚያስፈልጋቸው ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አሳሰቡ። ከሱዳን ሕዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሰብአዊ ርዳታ ያስፈልገዋል ተባለ። ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን በይገባኛል በሚወዛገቡባት አቢዬ ግዛት የሰፈረውን ሰላም አስከባሪ የሥራ ዘመን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አራዘመ። ደቡብ አፍሪካ በኬንያ በኩል ወደ ጁሐንስበርግ የተጓዙ ፍልስጤማውያንን ጉዳይ እንደምትመረምር አስታወቀች።
    Voir plus Voir moins
    15 min
  • የሕዳር 5 ቀን 2018 የዓለም ዜና
    Nov 14 2025
    -ታንዛኒያ ዉስጥ ባለፈዉ መስከረም የተደረገዉን አወዛጋቢ ምርጫ በሚቃወሙ የሐገሪቱ ዜጎች ላይ የተፈፀመዉ ግድያ እንደሚጣራ የሐገሪቱ ፕሬዝደንት አስታወቁ።ፕሬዝደንት ሳሚያ ሱሉሑ ሐሰን ዛሬ እንዳሉት የምርጫዉን ሒደት በመቃወማቸዉ ለታሰሩ ሰዎችም መንግሥታቸዉ ምሕርት ያደርጋል።የምርጫዉን -አፍሪቃ ዉስጥ በተገባደደዉ የግሪጎሪያኑ 2025 ዓመት የተሰራጨዉ የኮሌራ በሽታ 7ሺሕ ሰዎች ገደለ፤ ከ300 ሺሕ በላይ ለከፈ።-የሩሲያና የዩክሬን ጦር ኃይላት ዛሬ አንዱ የሌላዉን ግዛት በሰዉ አልባ አዉሮፕላንና በሚሳዬል ሲደበድቡ አነጉ።
    Voir plus Voir moins
    12 min
  • የሕዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
    Nov 13 2025
    በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጅንካ ከተማ የሄሞራጂክ ፊቨር በተባለ በሽታ 6 ሰዎች መሞታቸውን ተሰማ። የአፍሪካ ህብረት «በሰሜን ናይጄሪያ የተፈጸመ የዘር ማጥፋት ወንጀል የለም» ሲል አስተባበለ። እስራኤል በሐይል በያዘችው ምዕራባዊ የዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ የሰፈሩና «ፅንፈኛ» የተባሉ እስራኤላዉያን አንድ መስጊድን በእሳት ማቃጠላቸዉንና በመስጊዱ ግድግዳዎች ላይም «አጸያፊ» የተባሉ ፅሑፎች መጻፋቸው የፍልስጤማ ዜና አገልግሎት ዘገበ። ፈረንሳይ ከ10 ዓመታት በፊት በሽብር ጥቃት የተገደሉ 130 ዜጎችዋን ዛሬ ስትዘክር ዋለች።
    Voir plus Voir moins
    12 min
  • የህዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና
    Nov 12 2025
    ዛሬ ያስቻለዉ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ችሎት የቀድሞው የኢትዮጵያ የሰላም ሚንስትር ዴታ አቶ ታዬ ደንደአን ከ2 የክስ ጭብጦች ነጻ ሲያደርጋቸው በአንዱ ደግሞ ጥፋተኛ ብሏቸዋል። ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ መሆንዋን አስታወቀች። ጉባኤውን እንድታስተናግድ ያጸደቀውን የአፍሪቃ ተደራዳሪዎች ቡድንም አመሰገነች ። ስደተኞችን የጫነች አንዲት የፕላስቲክ ጀልባ በሊቢያ የባህር ዳርቻ ሰጥማ ቢያንስ 42 ስደተኞች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ጉዳይ ድርጅት በምህፃሩ IOM ዛሬ አስታወቀ። በግሪኳ ደሴት በጋቭዶስ አንዲት ስደተኞችን ያሳፈረች ጀልባ ሰጥማ ሦስት ሰዎች ሞቱ።
    Voir plus Voir moins
    12 min